Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ሩሲያ የባዮሎጂካል ሳይንስ የጥናትና ምርምር ማዕከል በጋራ ለማቋቋም ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በባዮሎጂካል ሳይንስ የጥናትና ምርምር ማዕከል በጋራ ለማቋቋም የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ቫለሪ ፋልኮቭ ጋር ተፈራርመዋል።

የሩሲያ ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ ከ 35 ዓመታት በላይ በስነ ህይወት ዙሪያ ጥናትና ምርምር ሲያደርጉ መቆየታቸው ተመላክቷል።

በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ÷የአሁኑ ስምምነት ከዚህ በፊት ሩሲያውያን ተመራማሪዎች ሲያካሂዱ የቆዩትን ጥናት አድማስ ለማስፋት ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ከዞህ ባለፈም ምርምሮቹ ተቋማዊ ባለቤትነት ኖሯቸው ኢትዮጵያ ከዘርፉ የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሀገራቱ ማዕከሉን በጋራ አቋቁመው ወደ ተግባር ሲገቡ በዘርፉ ያለው የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንደሚያስፋፋ ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.