የቀይ ባሕር ተለዋዋጭ የደኅንነት ጉዳዮችና ቀጣናዊ ትብብር ላይ ያተኮረ ጉባዔ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀይ ባሕር ተለዋዋጭ የደኅንነት ጉዳዮችና ቀጣናዊ ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ትኩረት ያደረገ ዓመታዊ ጉባዔ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡
ጉባዔው በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና መከላከያ ዋር ኮሌጅ ትብብር ነው የተዘጋጀው፡፡
“የቀይ ባሕር የደኅንነት ሁኔታ፤ ቀጣናዊ ምክክርና ትብብር መልክዓ-ፖለቲካዊ መጠላለፍ በበዛበት ዓለም” በሚል መሪ ሐሳብ ነው ጉባዔው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
የቀይ ባሕር ተለዋዋጭ የደኅንነት ጉዳዮችና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ ጉባዔው እንደሚመክር ይጠበቃል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!