Fana: At a Speed of Life!

የፓሌርሞ ኮንቬንሽን ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የተሳተፈችበት 20ኛው የፓሌርሞ ኮንቬንሽን ሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ጉባኤ ተጠናቋል፡፡

በርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በተገኙበት በዚህ ኮንፈረንስ በሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱአለም የተመራ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን ተሳትፏል፡፡

በኮንፈረንሱ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እና ህገ-ወጥ ስደተኞች ላይ ያተኮረ ውይይት መካሄዱ ተመላክቷል፡፡

በዚህ ወቅት የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዷለም÷ ኢትዮጵያ ህገ-ወጥ ስደትና ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመቆጣጠር የወሰደቻቸውን የፖሊሲ ማእቀፎች፣ ተቋማዊ አደረጃጀቶች እና የማስተካከያ እርምጃዎችን በመድረኩ አንስተዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን መግለጻቸውን የሰላም ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.