Fana: At a Speed of Life!

በቱርክ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ አንካራ በተካሄደው የሴቶችና የወንዶች የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል፡፡

በወንዶቹ አትሌት ሲሳይ ለማ 1 ሰዓት ከ1 ደቂቃ ከ9 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቋል፡፡

አትሌት ጪምዴሳ ደበሌ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አሸናፊ መሆኑንም ከዓለም አትሌቲክስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተጨማሪም አትሌት ዘውዲቱ አደራው በሴቶች ግማሽ ማራቶን ውድድር 1 ሰዓት ከ8 ደቂቃ ከ27 ሰከንድ በመግባት ማሸነፏም ነው የተሰማው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.