ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በመርሲሳይድ ደርቢ ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ለሊቨርፑል የማሸነፊያ ጎሎቹን ሞሀመድ ሳላህ ከእረፍት በኋላ በፍጹም ቅጣት ምት እና በጨዋታ አስቆጥሯል።
በጨዋታው ያሸነፈው ሊቨርፑል በ9 ጨዋታ 20 ነጥብ በመሰብሰብ የደረጃ ሰንጠረዡ ለጊዜው እየመራ ይገኛል።