Fana: At a Speed of Life!

ቱርክ ለቀጣናዊ ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ መፈለጓን እንደምትቀጥል ኤርዶሃን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶሃን የእስራኤል-ሃማስን ጦርነት ጨምሮ ሀገራቸው ለቀጣናዊ ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ መፈለጓን እንደምትቀጥል አመለከቱ።

ከዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር የስልክ ውይይት ያደረጉት ኤርዶሃን ለሩሲያ-ዩክሬንም ሆነ ለእስራኤል-ፍልስጤም እንዲሁም ለሰብዓዊ ቀውስ ቱርክ መፍትሄ የምታፈላልገው ሰላማዊ መንገድን በመከተል እንደሆነ መናገራቸውን የሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በኤክስ ባወጣው መረጃ ገልጿል።

ሰላማዊ መንገድን በመከተል ግጭትን ማቆም እንደሚቻል የምታምነው ቱርክ ሰላምን ለማረጋገጥ የምትችለውን ጥረት ሁሉ እንደምታደርግ ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንት ኤርዶሃን ከዩክሬን ፕሬዚዳንት በተጨማሪ ከሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን (ኔቶ) ዋና ጸሐፊ ጄን ስቶልተንበርግ እና ከኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ቲአርቲ ወርልድ ዘግቧል።

#Turkey #Israel #Palestine

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.