Fana: At a Speed of Life!

ከ245 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጥቅምት 2 እስከ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገ ክትትል ከ245 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉሙሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ 170 ሚሊየን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 75 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የወጭ በድምሩ 245 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች መያዛቸውን አስታውቋል፡፡

ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ ዕጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያየ ሀገር ገንዘቦች መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ኮንትሮባንዱን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 21 ተጠርጣሪዎችና 14 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.