Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የጣና ሞገዶቹ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአራተኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባሕርዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡

12፡00 ላይ በአዳማ ሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው ጨዋታ÷ ሀብታሙ ታደሰ የባሕርዳር ከተማን ሦስት ጎሎች በማስቆጠር ሃትሪክ ሠርቷል፡፡

ሃትሪኩም እስካሁን ባለው የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ውድድር የመጀመሪያው በመሆን ተመዝግቧል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም የጣና ሞገዶቹ ነጥባቸውን 7 በማድረስ ሦስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችለዋል፡፡

በአንጻሩ ወልቂጤ ከተማ ሁለት ነጥቦችን በመያዝ 13ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

9፡00 ላይ በተከናወነ የፕሪሚየር ሊጉ መርሐ ግብር ሐዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ያለምንም ግብ ተለያይተዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.