አቶ መላኩ አለበል ከጀርመን አምባሳደር ጋር መከሩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱሥትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አውራ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም የሁለቱ ሀገራትን ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከኢንዱሥትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የጀርመን መንግሥት በፋይናንስ ዘርፉ በተለይም ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን ልምድ ወደ አምራች ኢንዱሥትሪዎች ማስፋት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም ተወያይተዋል፡፡
በተጨማሪም በሣይበር ደኅንነት እና ዲጂታላይዜሽን ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸው ተመላክቷል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!