አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ኩሪፍቱ የአፍሪካ መንደርን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር እየተገነባ ያለውን የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር ጎብኝተዋል።
አምባሳደሩ ፥ የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር የአህጉሪቱ የፖለቲካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ የአፍሪካን የንግድ ምልክቶች እና እሴቶችን ለማስተዋወቅ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ባለቤት አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ፥ መንደሩ አፍሪካዊ ተልዕኮዎች በመፍጠር የተለያዩ አፍሪካ ሀገራትን ገጽታ በአንድ ቦታ ለማስተዋወቅ ይሰራል ብለዋል።
መንደሩ አፍሪካውያን በታታሪነታቸው አህጉራቸውን በተሻለ ሁኔታ ማስተዋወቅ እንደሚችሉ ማሳያ እንደሆነ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።