Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ኩሪፍቱ የአፍሪካ መንደርን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር እየተገነባ ያለውን የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር ጎብኝተዋል።

አምባሳደሩ ፥ የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር የአህጉሪቱ የፖለቲካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ የአፍሪካን የንግድ ምልክቶች እና እሴቶችን ለማስተዋወቅ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ባለቤት አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ፥ መንደሩ አፍሪካዊ ተልዕኮዎች በመፍጠር የተለያዩ አፍሪካ ሀገራትን ገጽታ በአንድ ቦታ ለማስተዋወቅ ይሰራል ብለዋል።

መንደሩ አፍሪካውያን በታታሪነታቸው አህጉራቸውን በተሻለ ሁኔታ ማስተዋወቅ እንደሚችሉ ማሳያ እንደሆነ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.