አትሌት ታምራት ቶላ የዘንድሮውን የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ታምራት ቶላ የዘንድሮውን የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር በአሸናፊነት አጠናቀቀ።
አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዘንድሮውን የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ሁለተኛ በመሆን አጠናቃለች።
በውድድሩ በወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያዊው አትሌት ታምራት ቶላ 2:04:58 በሆነ ሰዓት በመግባት በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ፤ ኬኒያዊው አትሌት አልበርት ኮሪሪ 2:06:57 በሆነ ሰዓት በመግባት ሁለተኛ ወጥቷል።
ሌላው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ 2:07:11 በሆነ ሰዓት በመግባት ሶስተኛ ደረጃን ይዟል።
በሴቶች ደግሞ ኬኒያዊቷ አትሌት ሄለን ኢቢሪ 2:27:23 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን ስታሸንፍ፤ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ 2:27:29 በሆነ ሰዓት ውድድሩን በማጠናቀቅ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች።
ከሶስተኛ እስከ ሰባተኛ ድረስ ያለውን ደረጃ በመያዝ ኬኒያውያን አትሌቶች ውድድሩን አጠናቀዋል።