Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ስለሺ ከአሜሪካው ሴናተር ማይክ ሮንድስ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ (ኢ/ር) ከአሜሪካው ሴናተር ማይክ ሮንድስጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ባለው የሁለትዮሽ እና ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአፍሪካ የእድገትና ዕድል ድንጋጌ (አጎዋ) ተጠቃሚነት እና ንግድ ዙሪያ መወያየታቸውን አምባሳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አተገባበር እና በሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭት ላይ መምከራቸውን አንስተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.