Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት አኪንዉሚ አዴሲና ጋር ተወያይተዋል፡፡

በሞሮኮ ማራካሽ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ፎረም ጉበኤ እየተሳተፉ የሚገኙት ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከፕሬዚዳንት አኪንዉሚ አዴሲና ጋር በቀጣይ የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ስርዓት ማሻሻያና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

በተጨማሪም በተለያዩ ስትራቴጅክ እቅዶች ላይ መምከራቸውን አስታውቀዋል

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.