በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ሲያሸንፍ ወላይታ ድቻና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም አቀፍ ውድድሮች ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ተጀምሯል፡፡
ወላይታ ድቻ እና ድሬዳዋ ከተማ 9 ሰዓት ላይ ባደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ለወላይታ ድቻ ቢንያም ፍቅሩ በ24ኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር÷ ድሬዳዋ ከተማን አቻ ያደረገችዋን ግብ ደግሞ ተመስገን ደረሰ በ61ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ሀምበሪቾ ዱራሜን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡
የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ግቦች ናትናኤል ገ/ጊዎርጊስ ፣ ጌታነህ ከበደ እና ምኞትደበበ አስቆጥረዋል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!