Fana: At a Speed of Life!

ጊዜያዊ የተኩሥ አቁም ሥምምነቱ ማብቃቱን ተከትሎ እስራዔል ጋዛን መደብደብ ቀጥላለች ተባለ

አዲስ አበባ፣ ኅዳር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ሥምምነቱ ማብቃቱን ተከትሎ እስራዔል ጋዛን መደብደብ መቀጠሏ ተገለጸ፡፡

ኳታር ፣ ግብፅ እና አሜሪካን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ አሸማጋዮች የተኩስ አቁም ሥምምነቱ እስከ ዛሬ እንዲራዘም ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ÷ እስራዔል ጋዛ ላይ የምታደርሰውን ጥቃት ለመቀጠል ዕቅድ እንዳላት አመላክተዋል፡፡

ከሰባተኛው ቀን የሰብዓዊነት ተኩሥ አቁም ሥምምነት በኋላ ዛሬ በቦንብና በመድፍ ታግዞ እንደገና የቀጠለው ጥቃት በንፁሐን ፍልሥጤማውያን ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ብሊንከን ማሳሰባቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

እስከዛሬዋ ዕለት ድረስ በጋዛ ከ15 ሺህ በላይ ፍልስጤማውያን ሕይወታቸውን ሲያጡ በእስራዔል ደግሞ የሟቾች ቁጥር 1 ሺህ 200 ያህል መድረሱን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.