Fana: At a Speed of Life!

በምስራቅ አፍሪካ ግዙፉ የንፋስ ሀይል ማመንጫ በሶማሌ ክልል ሊገነባ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 600 ሚሊየን ዶላር ወጭ የሚደረግበት 300 ሜጋ ዋት የሚያመነጭ የንፋስ ሀይል ማመንጫ በሶማሌ ክልል ሊገነባ ነው፡፡

ይህንን እውን ለማድረግ የገንዘብ ሚኒስቴር ከአሜአ ፓወር ኩባንያ ጋር የስምምነት ፊርማ ተፈራርሟል፡፡

በሶማሌ ክልል አይሻ አካባቢ የሚገነባው የንፋስ ሀይል ማመንጫ 300 ሜጋ ዋት ሀይል ማመንጨት የሚችል ነው ተብሏል፡፡

አጠቃላይ የንፋስ ሀይል ማመንጫው 600 ሚሊየን ዶላር ወጭ የሚደረግበት ሲሆን÷ አሜአ ፓወር በተሰኘ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ኩባንያ እንደሚሰራ ተጠቅሷል፡፡

ስምምነቱ በመንግስትና በግል አልሚዎች ማእቀፍ የሚሰራ ትልቁ ኢንቨስትመንት እንደሚሆን እንዲሁም በንፋስ ሀይል ማመንጫ ከምስራቅ አፍሪካ ግዝፉ ይሆናል መባሉን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ኢትዮጵያ በታዳሽ ሀይል ላይ መሰረት ላደረገ የሀይል አቅርቦት ስትራቴጂዋም ስምምነቱ ተጨማሪ ግብአት ይሆናል ነው የተባለው፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.