Fana: At a Speed of Life!

የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር አሶሳ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ገብተዋል።

አፈ ጉባዔው አሶሳ ሕዳሴ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ “ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል መሪ ሐሳብ በአሶሳ ማዕከል ለመንግሥት አመራሮች እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ማጠቃላያ ይሠጣሉ መባሉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.