Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች፡፡

የኢትዮጵያ ውሃ ዋና ስፖርት ብሔራዊ ቡድን በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው 8ኛው የዞን 3 አፍሪካ ውሃ ዋና ሻምፒዮና በማስተርስ ዋና ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አስመዝግቧል፡፡

ኢትዮጵያ በዞን 3 የአፍሪካ ውሃ ዋና ሻምፒዮና ውድድር በታዳጊ ወጣቶችና በማስተርስ ዋና ውድድር ተሳትፋ በ50 ሜትር ነፃ ቀዘፋ እና በ100 ሜትር ደረት ቀዘፋ በአትሌት እስከዳር አቻምየለህ አማካኝነት ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገቧን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.