Fana: At a Speed of Life!

ለገና በዓል ከታረደ በሬ ከ6 ግራም በላይ ወርቅ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለገና በዓል ከታረደ በሬ 6 ነጥብ 11 ግራም ወርቅ መገኘቱ ተሰምቷል፡፡

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለገና በዓል ቅርጫ ከታረደው በሬ ውስጥ ነው 6 ነጥብ 11 ግራም ወርቅ የተገኘው።

በወላይታ ባህል ለበዓል “አሞ” ወይም ቅርጫ ማረድ የተለመደ ሲሆን÷ ነገ ለሚከበረው የገና በዓል በታረደው የቅርጫ በሬ ውስጥም ወርቅ መገኘቱ ተገልጿል፡፡

የቅርጫ አባላቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ፥ የተገኘው ወርቅ የገና በዓል ስጦታ ነው።

በማህሌት ኡኩሞ

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.