Fana: At a Speed of Life!

በሊቢያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚደገፈው መንግስት ትሪፖሊን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27 (ኤፍቢሲ) በሊቢያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚደገፈው መንግስት ትሪፖሊን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ፡፡

በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው በትሪፖሊ የሚገኘው መንግስት ለጀነራል ካሊፊ ሀፍታር ታማኝ ከሆኑ ኃይሎች የከተማዋን የአውሮፕላን ማረፊያ መንጠቃቸው ተነግሩዋል፡፡

ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት እየሰጠ እንዳልነበረ ዘገባው አስታውሶ ተግባሩን ተንታኞች ለመንግሥት ትልቅ ድል ነው ብለውታል ፡፡

በዚህ ሂደትም የቱርክ ጦር ለትሪፖሊው መንግስት ድጋፍ ማድረጉ ተነግሩዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት አዲስ ዙር የዲፕሎማሲ ግንኙነት በመጀመሩ ከሁለቱ ወገኖች የተውጣጡ አመራሮች ለድርድር ወደ ውጭ ተጉዘዋል፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.