Fana: At a Speed of Life!

የሕንድ ንግድና ኢንቨስትመንት ልዑክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎቱን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕንድ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ልዑክ በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመን ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳለው ገልጿል፡፡

ልዑኩ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሮች ዳጋቶ ኩምቤ እና ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ጋር በአዲስ አበባ ተወያይቷል፡፡

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ በፋርማሲቲካል፣ በጨርቃጨርቅ፣ በአይ ሲ ቲ፣ በግብርና እና ሌሎችም ዘርፎች ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው ልዑኩ ማሳወቁን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

የሕንድ ንግድና ኢንቨስትመንት ልዑክ በኢትዮጵያ ለሚያከናውኑት ኢንቨስትመንት መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያድርግ ምክትል ኮሚሽነሮቹ አረጋግጠዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.