Fana: At a Speed of Life!

በትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምሥራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

አደጋው ዛሬ ከሰዓት 10 ሠዓት አካባቢ መድረሱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አረጋግጠዋል፡፡

አደጋው የደረሰውም ከአዲስ አበባ ወደ ቡታጅራ ይጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ 7 ሰዎችን ከጫነ “ባጃጅ” ጋር በመጋጨቱ ነው ብለዋል፡፡

የአምስቱ ተጓዦች ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉን እና በሁለቱ ላይም ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ጠቅሰዋል፡፡

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችም በወራቤ ኮምፕሪሄንሲቭ ሆስፒታል ሕክምና እያገኙ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በዮሐንስ ደርበው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.