Fana: At a Speed of Life!

የፌዴሬሽን ም/ቤትና የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት በትብብር ለመስራት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ም/ቤት እና የፌዴራል ፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡

የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት÷የተቋማቱ በጋራ መስራት ም/ቤቱ ሕገ-መንግስቱን በመተርጎም ሒደት ውስጥ የሚያጋጥሙትን ተግዳሮቶች ለመፍታት ያስችለዋል።

የሃብት አስተዳደርና የበጀት ክፍፍል ሥራው ውጤታማ እንዲሆን እንደሚያግዝ ጠቁመው÷ ከማንነትና ወሰን ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎችን በጥናት ተመስርቶ ምላሽ ለመስጠት እንደሚያስችልም ገልጸዋል፡፡

የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ በበኩላቸው÷ ኢንስቲትዩቱ በአቅም ግንባታ ላይ ሰፊ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ስምምነቱ እውነተኛ ፌዴራሊዝምን ለመተገበርና በመንግስታት በኩል ያለው ግንኙነት የተስተካከለ እንዲሆ ለማድረግ ያግዛል ተብሏል።

በዘመን በየነ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.