በኦሮሚያ ክልል 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር በበጋ መስኖ ስንዴ መልማቱ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጋ መስኖ ስንዴ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር በመስኖ ስንዴ መልማቱን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡
አቶ ሽመልስ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ከ105 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል፡፡
ከከባቢ ሁኔታ ወሳኝነትና ከዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ የተጀመሩ ሥራዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ጎን ለጎንም ባመረትነው ልክ የመቆጠብ እንቅስቃሴውን አጠንክረን እንቀጥላለን ብለዋል።