ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ያሰለጠናቸው 463 ተማሪዎች አስመረቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 463 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ከተመራቂዎች መካከል 131 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን አስተምሮ ሲያስምርቅ የዛሬው ለ12ኛ ጊዜ ነውም ተብሏል፡፡