በአቶ አደም ፋራህ የተመራ ልዑክ ጅቡቲ ገባ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ልዑክ ጅቡቲ ገብቷል።
ልዑኩ ጅቡቲ አምቡሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ አቀባበል ተደርጎለታል።
በጅቡቲ ቆይታቸውም የአር ፒ ፒ 45ኛ ዓመት ክብረ-በዓል ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡