135 ኢትዮጵያውያን ከሳኡዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 135 ኢትዮጵየዊያን በዛሬው እለት ከሳኡዲ አረቢያ መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከሳዑዲ ተመላሽ ኢትዮጵያውያኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፈያ ሲደርሱ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎች በቦታው ተገኘተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የዛሬዎቹን ጨምሮ በሳምንቱ ውስጥ ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የተመለሱ ዜጎቻችን ቁጥር 389መድረሱንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
ባሳለፍነው ሀሙስ 118 ኢትየጵያዊን ከሳኡዲ አረቢያ መመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን፥ በተመሳሳይ ባለፈው ማክሰኞም 136 ዜጎች ከሳኡዲ አረቢያ መመለሳቸው አይዘነጋም።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።