በመላ ሀገሪቱ ኃይል መቋረጡ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ከቀኑ 9 ሠዓት 46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
ሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል የተቋረጠ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን÷ ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ተብሏል።
የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
እስከዛ ድረስም ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ተቋሙ ጠይቋል፡፡