Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አንጎላ ሉዋንዳ የሚያደርገውን በረራ ወደ ዕለታዊ አሳደገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አንጎላ ሉዋንዳ ከተማ የሚያደርገውን በረራ ከሣምንታዊ ወደ ዕለታዊ ማሳደጉን አስታውቋል፡፡

የበረራው ወደ ዕለታዊ ማደግም ለመንገደኞች የተመቸ የጉዞ አማራጭ እንዲኖራቸው ያስችላል ብሏል አየር መንገዱ፡፡

ወደ አንጎላ እየተደረገ ያለው በረራ አራት አስርት ዓመታትን ማስቆጠሩን የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.