Fana: At a Speed of Life!

የኦሮሚያ ክልል መንግስትን የ30 ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ ዓውደ ርዕይ ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል መንግስትን የ30 ዓመታት ጉዞ የሚያስቃኝ ዓውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል ተከፍቷል።

በሥነ-ሥርዓቱ የክልልና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተዘጋጀው ዓውደ ርዕዩ እስከ መጪው ዓርብ ድረስ እንደሚቆይ ተመላክቷል፡፡

በመራኦል ከድር

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.