በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ማምረቻ ኢንዱስትሪን ጎበኘ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ልዑክ የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ማምረቻ ኢንዱስትሪ የሥራ እንቅስቃሴን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ከጉብኝቱ ቀጥሎም ፥ “ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ከየት ወዴት? ” በሚል ርዕሰ-ጉዳይ ተቋሙ ውጣ ውረዶችን በማለፍ እያስመዘገባቸው ያሉ ስኬቶችን የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቦ ምክክር እንደሚደረግበት ተመላክቷል፡፡