Fana: At a Speed of Life!

የዒድ አል ፈጥር በዓል ጨረቃ ሰኞ ማታ ከታየች ማክሰኞ ካልታየች ደግሞ ረቡዕ ይከበራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮው የዒድ አል ፈጥር በዓል ጨረቃ በመጪው ሰኞ ማታ ከታየች ማክሰኞ ካልታየች ደግሞ ረቡዕ አንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታውቋል።

ምክር ቤቱ 1 ሺህ 445ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም ፥ የዒድ አል ፈጥር በዓል ጨረቃ ሰኞ ማታ ከታየች ማክሰኞ ሚያዚያ 1 ቀን 2016 ካልታየች ደግሞ ረቡዕ ሚያዚያ 2 ቀን 2016 ዓ.ም አንደሚከበር አስታውቋል።

ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አልፈጥር በዓልን ሲያከብር በጾም ወቅት ሲያደርግ እንደነበረው እርስ በርስ በመደጋገፍና ለተቸገሩ ወገኖች በማካፈል ሊሆን እንደሚገባም አሳስቧል፡፡

በቤተልሄም መኳንት

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.