በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 345 ሽጉጥ ተያዘ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መነሻውን ምዕራብ ጎንደር ሸህዲ ሽንፋ አድርጎ ወደ ባህርዳር ከተማ ሊገባ የነበረ 345 ሽጉጥ መያዙን የባህርዳር-ጎንደር ኮማንድ ፖስት አስታወቀ።
ሕገ-ወጥ ሽጉጡ በተሽከርካሪ ላይ ተመሳስሎ በተሰራ ሻግ በድብቅ ተጭኖ ሲጓዝ በተደረገ ክትትል ምሽት 1 ሰዓት ላይ ባህርዳር ከተማ ሊገባ ሲል መያዙ ተገልጿል፡፡፡
ከድርጊቱ ጋር በተያያዘም የመኪናው ሹፌርና ረዳቱ በቁጥጥር ስር ውለው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
ሽጉጡ ሕገ-ወጥ የመሳሪያ ዝውውሩን በበላይነት በሚመራውና ለጊዜው በቁጥጥር ስር ባልዋለው በተሽከርካሪው ባለንብረት አማካኝነት ወደ ባህርዳር ገብቶ ለጥፋት ዓላማ ሊውል እንደነበርም ተጠቁሟል፡፡