Fana: At a Speed of Life!

የናይጄሪያ ልዑክ በኢትዮጵያ የመስኖ ስንዴ ልማት ዘርፍ የልምድ ልውውጥ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አመራሮችንና ባለሙያዎችን ያካተተው የናይጄሪያ ልዑክ በኢትዮጵያ በመስኖ ስንዴ ልማት ላይ የልምድ ልውውጥ አድርጓል፡፡

ከልምድ ልውውጡ በተጨማሪ ልዑኩ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አቢቹፍ ኛአ እና ቅምቢት ወረዳዎች በበኩታ ገጠም እየለማ ያለ የመስኖ ስንዴ ልማት እንቅስቃሴን ተመልክቷል፡፡

የግብርና ሚኒስትር ዴዔታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳስረዱት÷ በመስኖ ስንዴ ልማት ዘንድሮ 3 ሚሊየን ሄክታር በማልማት 120 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ ያለው ስራ አበረታች መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የስንዴ ልማት ሥራው ከውጪ የሚገባውን ስንዴ ማስቀረቱን ገልጸው፤ የምግብና ስርዓተ-ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድም የአርሶ አደሩን ገቢ ለማሳደግ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት እና ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.