Fana: At a Speed of Life!

አትሌት ጫላ ረጋሳ የቪዬና 2024 ማራቶንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጫላ ረጋሳ የቪዬና 2024 የማራቶን ውድድርን 2 ሠዓት ከ6 ደቂቃ ከ35 ሰከንድ በመግባት በበላይነት አጠናቀቀ፡፡

በተመሳሳይ በለንደን በተካሄደ የወንዶች የማራቶን ውድድር አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 2 ሠዓት ከ4 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል፡፡

እንዲሁም አትሌት ትዕግስት አሰፋ በለንደን የተካሄደውን የሴቶች ማራቶን ውድድር 2 ሠዓት ከ16 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡

በለንደን ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኬንያውያን አትሌቶች ሲያሸንፉ በቪዬና በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ውድድርም ኬንያውያን አትሌቶች 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.