Fana: At a Speed of Life!

 በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ19ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ቸርነት ጉግሳ ሁለቱንም የባህርዳር ከተማ ግቦች በፍጹም ቅጣት ምት ሲያስቆጥር÷ የወልቂጤን ብቸኛ ግብ ደግሞ ፉዓድ አብደላ አስቆጥሯል፡፡

በውጤቱ መሰረትም የጣና ሞገዶቹ ነጥባቸውን 37 በማድረስ  ወደ 4ኛ ደረጃ ከፍ ያሉ ሲሆን ÷ወልቂጤ ከተማ በ16 ነጥቦች ወራጅ ቀጠና ላይ ይገኛል፡፡

የክለቦቹ 19ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ የባህርዳር ከተማው የመሃል ክፍል ተጫዋች አለልኝ አዘነን ድንገተኛ ሕልፈት ተከትሎ መራዘሙ የሚታወስ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.