Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ በግንባታ ላይ ያለ ቤት ተደርምሶ በደረሰ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጊድ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በግንባታ ላይ ያለ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በደረሰ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

የክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አይዳ አወል እንዳሉት÷ በግንባታ ላይ ያለ የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ ነው አደጋው የተከሰተው፡፡

ሌሊት 11 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋም የ7 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ሥራ አስፈጻሚዋ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.