Fana: At a Speed of Life!

የሊቢያው ጠቅላይ ሚኒስትር ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሊቢያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አል-ዳባይባ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ምሽቱን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታም ከመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ፣ አኅጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.