Fana: At a Speed of Life!

የ8100 A 3ኛ ዙር ዕጣ ወጣ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ገቢ ለማሰባሰብ የሚካሄደው የ8100 A ዕጣ 3ኛ ዙር ዛሬ ወጣ።

በብሔራዊ ሎተሪ አዳራሽ በተካሄደ የዕጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት አሸናፊው ቁጥር የ ኤስ ኤም ኤስ ቁጥር 084492978 ሆኖ ወጥቷል።

የዕጣው ሽልማት 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ዘመናዊ ሃይሉክስ ፒክአፕ መኪና መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።

በስልክ መልዕክት የገቢ ማሰባሰቢያው የተጀመረው በዚህ ዓመት የካቲት ወር ላይ ሲሆን ለተጨማሪ ሶስት ወር የሚቆይ ይሆናል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.