Fana: At a Speed of Life!

አዲስ አበባና የቻይናዋ ቾንግኪንግ ከተማ የእህትማማች ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ እና የቻይናዋ ቾንግኪንግ ከተማ የእህትማማች ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በቻይና ቾንግኪንግ ከተማ የሥራ ጉብኝት አካሂዷል፡፡

በዚህ ወቅትም በአዲስ አበባ እና በቾንግቺንግ ከተማ መካከል የእህትማማች ስምምነት መፈረሙን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

የከተሞቹ አጋርነት በንግድ፣ በትምህርት እና በባህል ልውውጥ ያለውን ትብብር ማሳደግ እንደሚያስችል ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.