Fana: At a Speed of Life!

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትና ጨፌ ኦሮሚያ የኦሮሚያ ተወካይ ሴቶች የሰላም ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኦሮሚያ ክልልን ወክለው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ጨፌ ኦሮሚያ የሚገኙ ሴት አባላት የሰላም ጥሪ አቀረቡ።

የሰላም ጥሪው የቀረበው በኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ ታጣቂዎች ሲሆን÷ ታጣቂዎቹ የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሕብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ እናቶች ስንቄያቸውን በመያዝ ጠይቀዋል፡፡

የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ለሚመጡ ታጣቂዎች ለመቀበል መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባዔ ሰዓዳ አብድረህማን አረጋግጠዋል፡፡

በሀገር እድገት እና ብልፅግና ላይ በመሳተፍ እንደዜጋ የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም አስገንዝበዋል፡፡

በፈቲያ አብደላ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.