በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 368 ደረሰ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 232 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።
በዚህም በከተማዋ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 368 መድረሱን ነው የከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሪፓርት ያመለከተው።
ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ በ24 ሰዓታት ውስጥ በአዲስ አበባ 8 የኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል።
በሌላ በኩል ደግሞ በትላንትናው እለት 28 ሰዎች ከአዲስ አበባ ከኮሮና በሽታ አገግመዋል፡፡