ቢኒያም ዳዊት (ፕ/ር) የተመድ የሕጻናት መብቶች ኮሚቴ አባል ሆነው በድጋሚ ተመረጡ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቢኒያም ዳዊት (ፕ/ር) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሕጻናት መብቶች ኮሚቴ አባል ሆነው በድጋሚ ተመረጡ።
ቢኒያም ዳዊት (ፕ/ር) የተመድ የሕጻናት መብቶች ኮሚቴ አባል ሀገራት ዛሬ በኒውዮርክ ባካሄዱት ስብሰባ ነው በድጋሚ በአባልነት የተመረጡት፡፡
ቢኒያም (ፕ/ር) የኮሚቴው ነባር አባል ሲሆኑ÷በሊቀ-መንበርነት ማገልገላቸውንም በተመድ የኢትዮጵያ ተወካይ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡