Fana: At a Speed of Life!

የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ዝግጅቶች በከፍተኛ ርብርብ በመከናወን ላይ ይገኛሉ – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ዝግጅቶች በከፍተኛ ርብርብ በመከናወን ላይ ይገኛሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የችግኞች ተከላ እየተቃረበ እንደመሆኑ ዝግጅቶች በከፍተኛ ርብርብ በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

የተከላ ስፍራዎች ተለይተው በመዘጋጀት ላይ ሲሆኑ ችግኞችም በተከታታይነት በመፍላት ላይ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ዓመታዊ መርሃ ግብራችን የአካባቢ ጥበቃ ዘላቂነት መርህን የሚያስፋፋ፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚከላከል፣ የደን ጭፍጨፋን ጉዳት የሚቀለብስ፣ የመሬት መራቆትን የሚቀንስ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የማኅበረሰብ አባላት፣ ትምህርት ቤቶች እና ተቋማት በጋራ በመቆም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዛፎች እንዲተከሉ የተሰራበት ንቅናቄ ነው በማለት ገልጸዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.