Fana: At a Speed of Life!

ስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን የተከናወኑ ተግባራትን በስፋት አስተዋውቋል – በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የስትራይድ ኢትዮጵያ 2024 ኤክስፖ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ በምርምርና ኢኖቬሽን የተከናወኑ ተግባራትን በስፋት ያስተዋወቀ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።

ከግንቦት 11 እስከ 18 ቀን 2016 በሳይንስ ሙዚዬም ሲካሄድ የቆየው ስትራይድ ኢትዮጵያ 2024 ኤክስፖ የማጠናቀቂያ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በኤክስፖው በርካታ ልምዶች የተገኙበት በቴክኖሎጂ የታገዙ አዳዲስ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የታዩበትና የተበረታቱበት ነው፡፡

ግል ድርጅቶች ተሳትፎ የታየበት ኤክስፖእንደነበር ጠቅሰው÷ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ይሰራል ብለዋል።

የስራና ክሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው ÷የፈጠራ ሥራዎቹ ከግል ተጠቃሚነት ባሻገር የሥራ ዕድል ፈጠራ አመቺ ምህዳር የሚፈጥር ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

በማጠቃለያ መርሐ-ግብሩ ላይ ለዘርፍ አስተዋጽኦ ላደረጉና ተጨባጭ ውጤት ላስገኙ ሽልማትና ዕውቅና ተሰጥቷል።

በታሪኩ ለገሰ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.