Fana: At a Speed of Life!

ነገ መካሄድ በሚጀምረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የከተማ አስተዳደርና ክልላዊ የምክክር ምዕራፍ ተሳታፊዎች የሚተገብሯቸው ሥነ-ስርዓቶች

 

የስብሰባው ሥነ-ስርዓቶች

ይህ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት አካታች፣ አሳታፊና ሃሳቦች በግልጽ የሚንሸራሸሩበት ሂደት እንዲሆን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችንና ባለድርሻ አካላትን ወክለው የሚሳተፉ ተሳታፊዎች የሚከተሉትን የስብሰባ ሥነ-ስርዓቶች ማክበር ይኖርባቸዋል፡፡

1. ማንኛውም ተሳታፊ በነጻነት ሀሳቡን የመግለጽ መብት አለው።ሆኖም ተሳታፊዎች ከጥላቻ፣ ከአዋራጅ እና ከተንኳሽ ንግግሮችመቆጠብ፤

2. በምክክሩ ጊዜ መደማመጥን ከሚያውኩ፣ ሁከትን ከሚፈጥሩ እና መረጋጋትን ከሚነፍጉ ድርጊቶች እና ንግግሮች መቆጠብ፤

3. በጽሁፍ፣ በምልክት ወይም በድምጽ የጎንዮሽ ንግግር አለማድረግና ከተሳታፊዎች የሚቀርበውን ሃሳብ በአክብሮትና በጥሞና ማዳመጥ፤

4. እያንዳንዱ ተሳታፊ የሚሰጠውን ሃሳብና የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማክበር፣ በቅንነትና በታጋሽነት ማዳመጥ ፤

5. ሌላው ተሳታፊ ያቀረበውን ሃሳብ የመደገፍ ወይም የመቃወም ሁኔታ ሲኖር የሌሎች ተሳታፊዎችን መብት በሚያከብር መልኩ ማቅረብ፣

6. ተሳታፊው እድል ተሰጥቶት ሃሳቡን በመግለጽ ሂደት ላይ እያለ በማንኛውም ሁኔታ ያለማቋረጥ፤

7. የሰውን ክብር ከሚነኩ ነቀፌታዎች፣ ዘለፋዎች፣ ስብዕናን ከሚነኩ ንግግሮችና ድርጊቶች መቆጠብ፤

8. ሰዎች በሚያቀርቡት ሃሳብ እና አስተሳሰብ ባይስማሙ እንኳ ሃሳባቸውን እና አስተሳሰባቸውን ማክበር፤

9. የሚሰጠው ሀሳብ በቅን ልቦና ላይ የተመሠረተ ሆኖ ከውይይቱ አጀንዳ ጋር አግባብነት ያለው አጭር፣ ግልጽ ያልተደጋገመ እና የተፈቀደውን ጊዜ ባከበረ መልኩ መግለጽ፤

10. በሂደቱ ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ማብራሪያ እንዲሰጥ መጠየቅ ናቸው፡፡

እነዚህን የስብሰባ መሠረታዊ ሥነ-ስርዓቶች ተግባራዊ በማድረግ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ውጤታማ እንዲሆን የበኩልዎን ኋላፊነት ይወጡ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.