Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ የትጥቅ ብራንድ ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ ከሚገኝ የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር “ሀገሬ” የተሰኘ የራሱን ብራንድ ማስተዋወቁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ እንደገለጹት÷ ፌዴሬሽኑ ከተቋሙ ጋር ያደረገው የመግዛት እና የመሸጥ ስምምነት የጊዜ ገደብ የለውም፡፡

ፌዴሬሽኑ ያስተዋወቀው የትጥቅ ብራንድ በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አዲሱን የትጥቅ ብራንድ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከጊኒ ቢሳው እና ጅቡቲ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚጠቀመው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ፌደሬሽኑ በፓኪስታን የተሠራ የመጫወቻ ኳስ አስተዋውቋል።

በወርቅነህ ጋሻሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.