Fana: At a Speed of Life!

ሀሰተኛ ሰነድ የሚያዘጋጅን ግለሰብ ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ ሀሰተኛ ሰነድ የሚያዘጋጅን ግለሰብ ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 በሚገኘው የግለሰቡ መኖሪያ ቤት በተደረገ ብርበራ የ29 የመንግስትና የግል ተቋማት ክብ ማህተሞች፣ ብዛታቸው 26 የልዩ ልዩ የስራ ኃላፊ ቲተሮች በኤግዚቢትነት መያዙ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በግለሰቡ አማካኝነት የተዘጋጁ የወሳኝ ኩነት ሰነዶች ፣ የተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ፣ የሰራ ልምድ ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ፣ ልዩ ልዩ ደብዳቤዎችና ሰነዶችን በኤግዚቢትነት ይዞ ምርመራው መቀጠሉን አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ህገወጥ ተግባሩን ሲፈፅም እንደነበር በማስረጃ ተረጋግጧል ነው ያለው ፖሊስ፡፡

መንግስታዊ ፣ የግልና ሌሎች ተቋማትም ለልዩ ልዩ ጉዳዮች የሚቀርቡላቸውን ሰነዶችና መታወቂያዎች ትክክለኛነት የማረጋገጥ ተግባር ላይ ሊያተኩሩ እንደሚገባና ህብረተሰቡም መሰል ወንጀሎች ሲያጋጥመው ለፖሊስ ጥቆማ መስጠቱን ሊቀጥል እንደሚገባ አዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን በገጹ አስተላልፏል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.