Fana: At a Speed of Life!

ሐጎስ ገብረህይወት በ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ሐጎስ ገብረህይወት በዳይመንድ ሊግ የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ውድድር አሸንፏል፡፡

በውድድሩ 12፡36፡73 ሰዓት በመግባት ሲያሸንፍ ፥ በ5ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ሪከርድ ለመስበር በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ መግባቱ ተገልጿል፡፡

አትሌቱ በተሳተፈበት በዚህ ውድድርም በታሪክ የምንጊዜም ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ማስመዝገቡን ከዓለም አትሌቲክስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.