”ተፈጥሮ በምናንከባክበው ልክ መንፈሳችንን እና ጤናችንን ይንከባከባል”-ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 18 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)”ተፈጥሮ በምናንከባክበው ልክ መንፈሳችንን እና ጤናችንን ይንከባከባል” ሲሉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አዳነች አቤቤ ገለጹ
ወይዘሮ አዳነች በፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት÷ ”ዛሬ ሸገርን የማስዋብ እና እንጦጦ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ የደረሰበትን ደረጃ ሳይ ተደንቄያለው”ብለዋል።
”የዚህ ፕሮጀክት ፍጥነት፣ ውበት፣ ሰላም እና የሚሰጠው ንጹህ አየር በእጀጉ ያስደስታል÷በዚህ ስራ የተሳተፉ ሁሉ ምስጋና እና አድናቆታችን ይገባቸዋል”ም ነው ያሉት ።
እኛም በአቅራቢያችን ያሉትን የተፈጥሮ ሀብቶች እንዳቅማችን ለመንከባከብና ለማሳመር አምነን ቆርጠን ከተነሳን አካባቢያችንን ሁሉ ” ውብ እና ጤናማ ” ነው የምናደርገው ብለዋል።
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።